ኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጀነራል ኢንሹራንስ አ.ማ
Ethio Life and General Insurance S.C
የስብሰባ ጥሪ
ለኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጀነራል ኢንሹራንስ አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ
በኢትዮጵያ ንግድ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1243/2013 ፤ አንቀጽ 366 (1) ፣367(1) 370 እና 393 (1) እንዲሁም በማህበሩ መመስረቻ ፅሁፍ አንቀጽ 15 መሠረት የባለአክሲዮኖች 17ኛ ዓመታዊ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ቅዳሜ ታህሳስ 18 ቀን 2ዐ18 ዓ.ም በአዲስ አበባ ኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል ከጠዋቱ 2፡3ዐ ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል፡፡
በመሆኑም ውድ የማህበራችን ባለአክሲዮኖች በዕለቱ በጉባኤው ላይ ትገኙ ዘንድ የማህበሩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ጥሪውን በአክብሮት ያስተላልፋል፡፡
- የአክሲዮን ማህበሩን የሚመለከቱ ዋና ዋና መረጃዎች
- የማህበሩ ሥም ፡ ኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጀነራል ኢንሹራንስ አ.ማ
- የማህበህሩ ዋና መ/ቤት አድራሻ፡- አዲስ አበባ ፣ ቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ ዐ2 የቤት ቁጥር 659
- የማህበህሩ ድህረ ገፅ፡- www.eliginsurance.com.
- እ.ኤ.አ ጁን 3ዐ ቀን 2ዐ25 ላይ የማህበሩ የተፈረመ ገንዘብ፡- ብር 479,960,000.00
- እ.ኤ.አ ጁን 3ዐ ቀን 2025 ላይ የማህበሩ የተከፈለ ገንዘብ፡- ብር 405,296,000.00
- የንግድ ሥራ ፍቃድ ቁጥር፡ 013/08
- የንግድ የምዝገባ ቁጥር፡ KK/AA/2/0001326/2004
- የ17ኛው ዓመታዊ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎች
- የጉባኤዉን አጀንዳዎች ማጽደቅ፤
- የተተኪ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባል ሹመትን ማጽደቅ፤
- እስከ ህዳር 16 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የተደረጉትን የአክሲዮን ዝዉዉሮችን ማጽደቅ፤
- እ.ኤ.አ የ2024/25 የዳሬክተሮች ቦርድ ሪፖርት ላይ ተወያይቶ መወሰን፤
- እ.ኤ.አ የ2024/25 የዉጭ ኦዲተሮች ሪፖርት ላይ ተወያይቶ መወሰን፤
- እ.ኤ.አ የ2024/25 የሂሳብ ዓመት የትርፍ ድርሻ ክፍፍልን መወሰን፤
- እ.ኤ.አ ከ2025/26 ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ዓመታት የሚያገለግሉ የዉጭ አዲተሮችን
መሾም እና የአገልግሎት ክፍያቸውን መወሰን፤
- እ.ኤ.አ የ2024/25 የሂሳብ ዓመት የዳይሬክተሮች ቦርድ ዓመታዊ የሥራ ዋጋ መወሰን፤
- እ.ኤ.አ የ2025/26 የሂሳብ ዓመት የዳይሬክተሮች ቦርድ ወርሃዊ አበልን መወሰን፤
2.10 የዳይሬክተሮች ቦርድ ምልመላና አስመራጭ ኮሚቴ ሪፖርት ማዳመጥ፤
2.11 የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምርጫ ማካሄድ፤
ማሳሰቢያ
- በስብሰባዉ ላይ መገኝት የማይችሉ ባለአክሲዮኖች በንግድ ህጉ አንቀጽ 373 እና 377 መሰረት ጉባኤዉ ከሚካሄድበት ዕለት ሶስት ቀናት በፊት በመስቀል ፍላወር አካባቢ በሚገኝዉ የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጀነራል ኢንሹራንስ አ.ማ ዋና መ/ቤት 4ኛ ፎቅ አክሲዮን አስተዳደር ክፍል በመቅረብ ለዚሁ ዓላማ የተዘጋጀዉን የዉክልና ቅዕ ሞልተዉ በመፈረም ተወካይ አማካኝነት ጉባኤዉን መሳተፍ የሚችሉ መሆኑን በአክብሮት እንገልጻለን፡፡
- የኩባንያዉ ባለአክሲዮኖች ወይም ህጋዊ ወኪል በጉባኤዉ ለመሳተፍ ሲመጡ በኢትዮጵያ ካፒታል ገቢያ አዋጅ ላይ በተደነገገዉ መሠረት ተገቢዉን መረጃ ለማሟላት እንዲረዳን የኢትዮጵያ ዲጅታል መታወቂያ ካርድ (ፋይዳ) ዋናዉ እና ካፒ በመያዝ በጉባኤዉ ላይ መሳተፍ ይቻላል፡፡እንዲሁም ትዉልደ ኢትዮጵያዊ ሆነዉ የዉጭ ሀገር ዜግነት ያላቸዉ የኩባንያዉ ባለአክሲዮኖች ትዉልደ ኢትዮጵያዊ መሆናቸዉን የሚያረጋግጥ የታደሰ መታወቂያ/ቢጫ ካርድ ዜግነት ይዘዉ መቅረብ እንዳለባቸዉ በአክብሮት እናሳዉቃለን፡፡
- የዉክልና ቅጽ በዋና መ/ቤቱ በአካል ተገኝቶ ያልሞላ ባለአክሲዮኖች ህጋዊ ተወካዮች ስብሰባዉን ለመካፈል የሚያስችል ግልጽ ሥልጣን የሚያሳይ በሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ አገልግሎት ወይም አግባብ ባለዉ አካል የተመዘገበ ዉክልና ይዘዉ መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
በዳይሬክተሮች ቦርድ ትዕዛዝ
ኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጀነራል ኢንሹራንስ አ.ማ
+251-011-554-96-51/+251-011-557-17-81
አዲስ አበባ፣ኢትዮጵያ
